ዛሬ በፕላንና ልማት ሚኒስቴር የዘላቂ የልማት ግቦች የቴክኒካል ኮሚቴ አባላት ጋር በቀጣይ ስራዎች ላይ ተግባራዊነት ዙሪያ የተደረገው ውይይት ጠቃሚ እንደነበር ተገልጿል።
የቴክኒካል ኮሚቴው አባላት ከፌዴራል ሚኒስቴር አስፈፃሚ የመንግስት ተቋማት፣ ከልማት አጋሮች፣ ከሲቪክ ማህበረሰብ ድርጅቶች፣ ከከፍተኛ ትምህርት ተቋማትና ከግል ዘርፍ የተውጣጡ ሲሆን የዘላቂ ልማት ግቦችን ለማሳካት በተቀመጠው ፍኖተ ካርታ በተቀናጀ ስትራቴጂ በጋራ መስራት እንደሚገባ ተገልጿል።
የፕላንና ልማት ሚኒስቴር ሚንስትር ዲኤታ አቶ በረከት ፍስሃፅዮን ውይይቱ በኢትዮጵያ የዘላቂ የልማት ግቦች ሁሉን ባካተተ መንገድና በዘላቂነት ውጤታማ ሆኖ እንዲተገበር በቁርጠኝነት እየተሰራ መሆኑን ማሳያ መሆኑን አስረድተዋል።